إِذَا ٱلشَّمْسُ كُوِّرَتْ
Itha ashshamsu kuwwirat
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
The Overthrowing
إِذَا ٱلشَّمْسُ كُوِّرَتْ
Itha ashshamsu kuwwirat
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتْ
Wa-itha annujoomu inkadarat
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجِبَالُ سُيِّرَتْ
Wa-itha aljibalu suyyirat
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْعِشَارُ عُطِّلَتْ
Wa-itha alAAisharu AAuttilat
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْوُحُوشُ حُشِرَتْ
Wa-itha alwuhooshu hushirat
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْبِحَارُ سُجِّرَتْ
Wa-itha albiharu sujjirat
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتْ
Wa-itha annufoosu zuwwijat
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْمَوْءُۥدَةُ سُئِلَتْ
Wa-itha almawoodatu su-ilat
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
بِأَىِّ ذَنۢبٍ قُتِلَتْ
Bi-ayyi thanbin qutilat
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتْ
Wa-itha assuhufunushirat
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ كُشِطَتْ
Wa-itha assamao kushitat
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجَحِيمُ سُعِّرَتْ
Wa-itha aljaheemu suAAAAirat
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ
Wa-itha aljannatu ozlifat
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
عَلِمَتْ نَفْسٌ مَّآ أَحْضَرَتْ
AAalimat nafsun ma ahdarat
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلْخُنَّسِ
Fala oqsimu bilkhunnas
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ٱلْجَوَارِ ٱلْكُنَّسِ
Aljawari alkunnas
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ
Wallayli itha AAasAAas
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
وَٱلصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ
Wassubhi ithatanaffas
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
إِنَّهُۥ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ
Innahu laqawlu rasoolin kareem
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
ذِى قُوَّةٍ عِندَ ذِى ٱلْعَرْشِ مَكِينٍ
Thee quwwatin AAinda theealAAarshi makeen
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
مُّطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ
MutaAAin thamma ameen
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍ
Wama sahibukum bimajnoon
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
وَلَقَدْ رَءَاهُ بِٱلْأُفُقِ ٱلْمُبِينِ
Walaqad raahu bilofuqialmubeen
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
وَمَا هُوَ عَلَى ٱلْغَيْبِ بِضَنِينٍ
Wama huwa AAala alghaybi bidaneen
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَـٰنٍ رَّجِيمٍ
Wama huwa biqawli shaytaninrajeem
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ
Faayna tathhaboon
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَـٰلَمِينَ
In huwa illa thikrun lilAAalameen
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
لِمَن شَآءَ مِنكُمْ أَن يَسْتَقِيمَ
Liman shaa minkum an yastaqeem
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلْعَـٰلَمِينَ
Wama tashaoona illa anyashaa Allahu rabbu alAAalameen
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡