عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
AAabasa watawalla
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
He Frowned
عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
AAabasa watawalla
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
أَن جَآءَهُ ٱلْأَعْمَىٰ
An jaahu al-aAAma
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
Wama yudreeka laAAallahu yazzakka
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكْرَىٰٓ
Aw yaththakkaru fatanfaAAahu aththikra
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
أَمَّا مَنِ ٱسْتَغْنَىٰ
Amma mani istaghna
የተብቃቃው ሰውማ፤
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
Faanta lahu tasadda
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
وَمَا عَلَيْكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
Wama AAalayka alla yazzakka
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسْعَىٰ
Waamma man jaaka yasAAa
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
وَهُوَ يَخْشَىٰ
Wahuwa yakhsha
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
فَأَنتَ عَنْهُ تَلَهَّىٰ
Faanta AAanhu talahha
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
كَلَّآ إِنَّهَا تَذْكِرَةٌ
Kalla innaha tathkira
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
Faman shaa thakarah
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
فِى صُحُفٍ مُّكَرَّمَةٍ
Fee suhufin mukarrama
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
مَّرْفُوعَةٍ مُّطَهَّرَةٍۭ
MarfooAAatin mutahhara
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
بِأَيْدِى سَفَرَةٍ
Bi-aydee safara
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
كِرَامٍۭ بَرَرَةٍ
Kiramin barara
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
قُتِلَ ٱلْإِنسَـٰنُ مَآ أَكْفَرَهُۥ
Qutila al-insanu ma akfarah
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
مِنْ أَىِّ شَىْءٍ خَلَقَهُۥ
Min ayyi shay-in khalaqah
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
مِن نُّطْفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
Min nutfatin khalaqahu faqaddarah
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
Thumma assabeela yassarah
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقْبَرَهُۥ
Thumma amatahu faaqbarah
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
Thumma itha shaa ansharah
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
كَلَّا لَمَّا يَقْضِ مَآ أَمَرَهُۥ
Kalla lamma yaqdi maamarah
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
فَلْيَنظُرِ ٱلْإِنسَـٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
Falyanthuri al-insanuila taAAamih
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
أَنَّا صَبَبْنَا ٱلْمَآءَ صَبًّا
Anna sababna almaasabba
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ثُمَّ شَقَقْنَا ٱلْأَرْضَ شَقًّا
Thumma shaqaqna al-arda shaqqa
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
فَأَنۢبَتْنَا فِيهَا حَبًّا
Faanbatna feeha habba
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
وَعِنَبًا وَقَضْبًا
WaAAinaban waqadba
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
وَزَيْتُونًا وَنَخْلًا
Wazaytoonan wanakhla
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
وَحَدَآئِقَ غُلْبًا
Wahada-iqa ghulba
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
وَفَـٰكِهَةً وَأَبًّا
Wafakihatan waabba
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
مَّتَـٰعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَـٰمِكُمْ
MataAAan lakum wali-anAAamikum
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
Fa-itha jaati assakhkha
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
يَوْمَ يَفِرُّ ٱلْمَرْءُ مِنْ أَخِيهِ
Yawma yafirru almaro min akheeh
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
Waommihi waabeeh
ከናቱም ካባቱም፤
وَصَـٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
Wasahibatihi wabaneeh
ከሚስቱም ከልጁም፤
لِكُلِّ ٱمْرِئٍ مِّنْهُمْ يَوْمَئِذٍ شَأْنٌ يُغْنِيهِ
Likulli imri-in minhum yawma-ithinsha/nun yughneeh
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ مُّسْفِرَةٌ
Wujoohun yawma-ithin musfira
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ضَاحِكَةٌ مُّسْتَبْشِرَةٌ
Dahikatun mustabshira
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ عَلَيْهَا غَبَرَةٌ
Wawujoohun yawma-ithin AAalayhaghabara
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
تَرْهَقُهَا قَتَرَةٌ
Tarhaquha qatara
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
أُو۟لَـٰٓئِكَ هُمُ ٱلْكَفَرَةُ ٱلْفَجَرَةُ
Ola-ika humu alkafaratu alfajara
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡