إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتْ
Itha assamao infatarat
ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
The Cleaving
إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتْ
Itha assamao infatarat
ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتْ
Wa-itha alkawakibu intatharat
ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْبِحَارُ فُجِّرَتْ
Wa-itha albiharu fujjirat
ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْقُبُورُ بُعْثِرَتْ
Wa-itha alqubooru buAAthirat
መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
عَلِمَتْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ وَأَخَّرَتْ
AAalimat nafsun ma qaddamatwaakhkharat
ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
يَـٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَـٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلْكَرِيمِ
Ya ayyuha al-insanu magharraka birabbika alkareem
አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
ٱلَّذِى خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ
Allathee khalaqaka fasawwakafaAAadalak
በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
فِىٓ أَىِّ صُورَةٍ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ
Fee ayyi sooratin ma shaarakkabak
በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
كَلَّا بَلْ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ
Kalla bal tukaththiboona biddeen
ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
وَإِنَّ عَلَيْكُمْ لَحَـٰفِظِينَ
Wa-inna AAalaykum lahafitheen
በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
كِرَامًا كَـٰتِبِينَ
Kiraman katibeen
የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
يَعْلَمُونَ مَا تَفْعَلُونَ
YaAAlamoona ma tafAAaloon
የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
إِنَّ ٱلْأَبْرَارَ لَفِى نَعِيمٍ
Inna al-abrara lafee naAAeem
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
وَإِنَّ ٱلْفُجَّارَ لَفِى جَحِيمٍ
Wa-inna alfujjara lafee jaheem
ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
يَصْلَوْنَهَا يَوْمَ ٱلدِّينِ
Yaslawnaha yawma addeen
በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
وَمَا هُمْ عَنْهَا بِغَآئِبِينَ
Wama hum AAanha bigha-ibeen
እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ
Wama adraka ma yawmu addeeni
የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
ثُمَّ مَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ
Thumma ma adraka mayawmu addeen
ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
يَوْمَ لَا تَمْلِكُ نَفْسٌ لِّنَفْسٍ شَيْـًٔا ۖ وَٱلْأَمْرُ يَوْمَئِذٍ لِّلَّهِ
Yawma la tamliku nafsun linafsinshay-an wal-amru yawma-ithin lillah
(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡