وَٱلْعَـٰدِيَـٰتِ ضَبْحًا
WalAAadiyati dabha
እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
The Courser
وَٱلْعَـٰدِيَـٰتِ ضَبْحًا
WalAAadiyati dabha
እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
فَٱلْمُورِيَـٰتِ قَدْحًا
Falmooriyati qadha
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
فَٱلْمُغِيرَٰتِ صُبْحًا
Falmugheerati subha
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
فَأَثَرْنَ بِهِۦ نَقْعًا
Faatharna bihi naqAAa
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
فَوَسَطْنَ بِهِۦ جَمْعًا
Fawasatna bihi jamAAa
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
إِنَّ ٱلْإِنسَـٰنَ لِرَبِّهِۦ لَكَنُودٌ
Inna al-insana lirabbihi lakanood
ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
وَإِنَّهُۥ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٌ
Wa-innahu AAala thalikalashaheed
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
وَإِنَّهُۥ لِحُبِّ ٱلْخَيْرِ لَشَدِيدٌ
Wa-innahu lihubbi alkhayri lashadeed
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
۞ أَفَلَا يَعْلَمُ إِذَا بُعْثِرَ مَا فِى ٱلْقُبُورِ
Afala yaAAlamu itha buAAthira mafee alquboor
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
وَحُصِّلَ مَا فِى ٱلصُّدُورِ
Wahussila ma fee assudoor
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
إِنَّ رَبَّهُم بِهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّخَبِيرٌۢ
Inna rabbahum bihim yawma-ithinlakhabeer
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡