عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
AAamma yatasaaloon
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
The Tidings
عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
AAamma yatasaaloon
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلْعَظِيمِ
AAani annaba-i alAAatheem
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
ٱلَّذِى هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ
Allathee hum feehi mukhtalifoon
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
Kalla sayaAAlamoon
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
Thumma kalla sayaAAlamoon
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
أَلَمْ نَجْعَلِ ٱلْأَرْضَ مِهَـٰدًا
Alam najAAali al-arda mihada
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
وَٱلْجِبَالَ أَوْتَادًا
Waljibala awtada
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
وَخَلَقْنَـٰكُمْ أَزْوَٰجًا
Wakhalaqnakum azwaja
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًا
WajaAAalna nawmakum subata
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ لِبَاسًا
WajaAAalna allayla libasa
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشًا
WajaAAalna annaharamaAAasha
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًا شِدَادًا
Wabanayna fawqakum sabAAan shidada
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
وَجَعَلْنَا سِرَاجًا وَهَّاجًا
WajaAAalna sirajan wahhaja
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
وَأَنزَلْنَا مِنَ ٱلْمُعْصِرَٰتِ مَآءً ثَجَّاجًا
Waanzalna mina almuAAsiratimaan thajjaja
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
لِّنُخْرِجَ بِهِۦ حَبًّا وَنَبَاتًا
Linukhrija bihi habban wanabata
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
وَجَنَّـٰتٍ أَلْفَافًا
Wajannatin alfafa
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
إِنَّ يَوْمَ ٱلْفَصْلِ كَانَ مِيقَـٰتًا
Inna yawma alfasli kana meeqata
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
يَوْمَ يُنفَخُ فِى ٱلصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًا
Yawma yunfakhu fee assoorifata/toona afwaja
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتْ أَبْوَٰبًا
Wafutihati assamao fakanatabwaba
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
وَسُيِّرَتِ ٱلْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا
Wasuyyirati aljibalu fakanatsaraba
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًا
Inna jahannama kanat mirsada
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
لِّلطَّـٰغِينَ مَـَٔابًا
Littagheena maaba
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
لَّـٰبِثِينَ فِيهَآ أَحْقَابًا
Labitheena feeha ahqaba
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًا وَلَا شَرَابًا
La yathooqoona feehabardan wala sharaba
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
إِلَّا حَمِيمًا وَغَسَّاقًا
Illa hameeman waghassaqa
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
جَزَآءً وِفَاقًا
Jazaan wifaqa
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا۟ لَا يَرْجُونَ حِسَابًا
Innahum kanoo la yarjoona hisaba
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
وَكَذَّبُوا۟ بِـَٔايَـٰتِنَا كِذَّابًا
Wakaththaboo bi-ayatinakiththaba
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
وَكُلَّ شَىْءٍ أَحْصَيْنَـٰهُ كِتَـٰبًا
Wakulla shay-in ahsaynahu kitaba
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
فَذُوقُوا۟ فَلَن نَّزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا
Fathooqoo falan nazeedakum illaAAathaba
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا
Inna lilmuttaqeena mafaza
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
حَدَآئِقَ وَأَعْنَـٰبًا
Hada-iqa waaAAnaba
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًا
WakawaAAiba atraba
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
وَكَأْسًا دِهَاقًا
Waka/san dihaqa
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
لَّا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا كِذَّٰبًا
La yasmaAAoona feeha laghwanwala kiththaba
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
جَزَآءً مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابًا
Jazaan min rabbika AAataan hisaba
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
رَّبِّ ٱلسَّمَـٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ٱلرَّحْمَـٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًا
Rabbi assamawati wal-ardiwama baynahuma arrahmani layamlikoona minhu khitaba
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
يَوْمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلْمَلَـٰٓئِكَةُ صَفًّا ۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحْمَـٰنُ وَقَالَ صَوَابًا
Yawma yaqoomu arroohu walmala-ikatusaffan la yatakallamoona illa man athinalahu arrahmanu waqala sawaba
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
ذَٰلِكَ ٱلْيَوْمُ ٱلْحَقُّ ۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
Thalika alyawmu alhaqqu famanshaa ittakhatha ila rabbihi maaba
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
إِنَّآ أَنذَرْنَـٰكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنظُرُ ٱلْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلْكَافِرُ يَـٰلَيْتَنِى كُنتُ تُرَٰبًۢا
Inna antharnakum AAathabanqareeban yawma yanthuru almaro ma qaddamatyadahu wayaqoolu alkafiru ya laytanee kuntuturaba
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡