وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ
Wallayli itha yaghsha
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
The Night
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ
Wallayli itha yaghsha
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
Wannahari itha tajalla
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ
Wama khalaqa aththakarawal-ontha
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
إِنَّ سَعْيَكُمْ لَشَتَّىٰ
Inna saAAyakum lashatta
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
فَأَمَّا مَنْ أَعْطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
Faamma man aAAta wattaqa
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
وَصَدَّقَ بِٱلْحُسْنَىٰ
Wasaddaqa bilhusna
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْيُسْرَىٰ
Fasanuyassiruhu lilyusra
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسْتَغْنَىٰ
Waamma man bakhila wastaghna
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
وَكَذَّبَ بِٱلْحُسْنَىٰ
Wakaththaba bilhusna
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْعُسْرَىٰ
Fasanuyassiruhu lilAAusra
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَمَا يُغْنِى عَنْهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
Wama yughnee AAanhu maluhu ithataradda
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
إِنَّ عَلَيْنَا لَلْهُدَىٰ
Inna AAalayna lalhuda
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
وَإِنَّ لَنَا لَلْـَٔاخِرَةَ وَٱلْأُولَىٰ
Wa-inna lana lal-akhirata wal-oola
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
فَأَنذَرْتُكُمْ نَارًا تَلَظَّىٰ
Faanthartukum naran talaththa
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
لَا يَصْلَىٰهَآ إِلَّا ٱلْأَشْقَى
La yaslaha illaal-ashqa
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
ٱلَّذِى كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
Allathee kaththaba watawalla
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلْأَتْقَى
Wasayujannabuha al-atqa
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِى يُؤْتِى مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
Allathee yu/tee malahuyatazakka
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعْمَةٍ تُجْزَىٰٓ
Wama li-ahadin AAindahu minniAAmatin tujza
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
إِلَّا ٱبْتِغَآءَ وَجْهِ رَبِّهِ ٱلْأَعْلَىٰ
Illa ibtighaa wajhi rabbihial-aAAla
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
وَلَسَوْفَ يَرْضَىٰ
Walasawfa yarda
ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡