إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتْ
Itha assamao inshaqqat
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
The Sundering
إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتْ
Itha assamao inshaqqat
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
Waathinat lirabbiha wahuqqat
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
وَإِذَا ٱلْأَرْضُ مُدَّتْ
Wa-itha al-ardu muddat
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ
Waalqat ma feeha watakhallat
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
Waathinat lirabbiha wahuqqat
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
يَـٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَـٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًا فَمُلَـٰقِيهِ
Ya ayyuha al-insanuinnaka kadihun ila rabbika kadhanfamulaqeeh
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
فَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَـٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ
Faama man ootiya kitabahubiyameenih
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًا يَسِيرًا
Fasawfa yuhasabu hisabanyaseera
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًا
Wayanqalibu ila ahlihi masroora
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
وَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَـٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهْرِهِۦ
Waamma man ootiya kitabahu waraathahrih
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يَدْعُوا۟ ثُبُورًا
Fasawfa yadAAoo thuboora
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
وَيَصْلَىٰ سَعِيرًا
Wayasla saAAeera
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
إِنَّهُۥ كَانَ فِىٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًا
Innahu kana fee ahlihi masroora
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
Innahu thanna an lan yahoor
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
بَلَىٰٓ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرًا
Bala inna rabbahu kana bihi baseera
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلشَّفَقِ
Fala oqsimu bishshafaq
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
وَٱلَّيْلِ وَمَا وَسَقَ
Wallayli wama wasaq
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
وَٱلْقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ
Walqamari itha ittasaq
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٍ
Latarkabunna tabaqan AAan tabaq
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
Fama lahum la yu/minoon
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
وَإِذَا قُرِئَ عَلَيْهِمُ ٱلْقُرْءَانُ لَا يَسْجُدُونَ ۩
Wa-itha quri-a AAalayhimu alqur-anula yasjudoon
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ يُكَذِّبُونَ
Bali allatheena kafaroo yukaththiboon
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
وَٱللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوعُونَ
Wallahu aAAlamu bimayooAAoon
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
فَبَشِّرْهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ
Fabashshirhum biAAathabin aleem
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّـٰلِحَـٰتِ لَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍۭ
Illa allatheena amanoowaAAamiloo assalihati lahum ajrun ghayrumamnoon
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡