لَآ أُقْسِمُ بِهَـٰذَا ٱلْبَلَدِ
La oqsimu bihatha albalad
በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡
The City
لَآ أُقْسِمُ بِهَـٰذَا ٱلْبَلَدِ
La oqsimu bihatha albalad
በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡
وَأَنتَ حِلٌّۢ بِهَـٰذَا ٱلْبَلَدِ
Waanta hillun bihatha albalad
አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡
وَوَالِدٍ وَمَا وَلَدَ
Wawalidin wama walad
በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡
لَقَدْ خَلَقْنَا ٱلْإِنسَـٰنَ فِى كَبَدٍ
Laqad khalaqna al-insana feekabad
ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡
أَيَحْسَبُ أَن لَّن يَقْدِرَ عَلَيْهِ أَحَدٌ
Ayahsabu an lan yaqdira AAalayhi ahad
በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?
يَقُولُ أَهْلَكْتُ مَالًا لُّبَدًا
Yaqoolu ahlaktu malan lubada
«ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ» ይላል፡፡
أَيَحْسَبُ أَن لَّمْ يَرَهُۥٓ أَحَدٌ
Ayahsabu an lam yarahu ahad
አንድም ያላየው መኾኑን ያስባልን?
أَلَمْ نَجْعَل لَّهُۥ عَيْنَيْنِ
Alam najAAal lahu AAaynayn
ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?
وَلِسَانًا وَشَفَتَيْنِ
Walisanan washafatayn
ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፡፡
وَهَدَيْنَـٰهُ ٱلنَّجْدَيْنِ
Wahadaynahu annajdayn
ሁለትን መንገዶችም አልመራነውምን?
فَلَا ٱقْتَحَمَ ٱلْعَقَبَةَ
Fala iqtahama alAAaqaba
ዓቀበቲቱንም አልወጣም፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْعَقَبَةُ
Wama adraka maalAAaqaba
ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
فَكُّ رَقَبَةٍ
Fakku raqaba
(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡
أَوْ إِطْعَـٰمٌ فِى يَوْمٍ ذِى مَسْغَبَةٍ
Aw itAAamun fee yawmin theemasghaba
ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡
يَتِيمًا ذَا مَقْرَبَةٍ
Yateeman tha maqraba
የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤
أَوْ مِسْكِينًا ذَا مَتْرَبَةٍ
Aw miskeenan tha matraba
ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡
ثُمَّ كَانَ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلْمَرْحَمَةِ
Thumma kana mina allatheena amanoowatawasaw bissabri watawasaw bilmarhama
(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡
أُو۟لَـٰٓئِكَ أَصْحَـٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ
Ola-ika as-habualmaymana
እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ بِـَٔايَـٰتِنَا هُمْ أَصْحَـٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ
Wallatheena kafaroo bi-ayatinahum as-habu almash-ama
እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
عَلَيْهِمْ نَارٌ مُّؤْصَدَةٌۢ
AAalayhim narun mu/sada
በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡