وَٱلصَّـٰٓفَّـٰتِ صَفًّا
Wassaffati saffa
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Those who set the Ranks
وَٱلصَّـٰٓفَّـٰتِ صَفًّا
Wassaffati saffa
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجْرًا
Fazzajirati zajra
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
فَٱلتَّـٰلِيَـٰتِ ذِكْرًا
Fattaliyati thikra
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
إِنَّ إِلَـٰهَكُمْ لَوَٰحِدٌ
Inna ilahakum lawahid
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
رَّبُّ ٱلسَّمَـٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا وَرَبُّ ٱلْمَشَـٰرِقِ
Rabbu assamawati wal-ardiwama baynahuma warabbu almashariq
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنْيَا بِزِينَةٍ ٱلْكَوَاكِبِ
Inna zayyanna assamaaaddunya bizeenatin alkawakib
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
وَحِفْظًا مِّن كُلِّ شَيْطَـٰنٍ مَّارِدٍ
Wahifthan min kulli shaytaninmarid
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلْمَلَإِ ٱلْأَعْلَىٰ وَيُقْذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٍ
La yassammaAAoona ila almala-ial-aAAla wayuqthafoona min kulli janib
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
دُحُورًا ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ وَاصِبٌ
Duhooran walahum AAathabun wasib
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
إِلَّا مَنْ خَطِفَ ٱلْخَطْفَةَ فَأَتْبَعَهُۥ شِهَابٌ ثَاقِبٌ
Illa man khatifa alkhatfatafaatbaAAahu shihabun thaqib
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
فَٱسْتَفْتِهِمْ أَهُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَم مَّنْ خَلَقْنَآ ۚ إِنَّا خَلَقْنَـٰهُم مِّن طِينٍ لَّازِبٍۭ
Fastaftihim ahum ashaddu khalqan amman khalaqna inna khalaqnahum min teeninlazib
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
بَلْ عَجِبْتَ وَيَسْخَرُونَ
Bal AAajibta wayaskharoon
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
وَإِذَا ذُكِّرُوا۟ لَا يَذْكُرُونَ
Wa-itha thukkiroo la yathkuroon
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
وَإِذَا رَأَوْا۟ ءَايَةً يَسْتَسْخِرُونَ
Wa-itha raaw ayatanyastaskhiroon
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
وَقَالُوٓا۟ إِنْ هَـٰذَآ إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ
Waqaloo in hatha illasihrun mubeen
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
أَءِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَـٰمًا أَءِنَّا لَمَبْعُوثُونَ
A-itha mitna wakunnaturaban waAAithaman a-innalamabAAoothoon
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلْأَوَّلُونَ
Awa abaona al-awwaloon
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
قُلْ نَعَمْ وَأَنتُمْ دَٰخِرُونَ
Qul naAAam waantum dakhiroon
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
فَإِنَّمَا هِىَ زَجْرَةٌ وَٰحِدَةٌ فَإِذَا هُمْ يَنظُرُونَ
Fa-innama hiya zajratun wahidatunfa-itha hum yanthuroon
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
وَقَالُوا۟ يَـٰوَيْلَنَا هَـٰذَا يَوْمُ ٱلدِّينِ
Waqaloo ya waylana hathayawmu addeen
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
هَـٰذَا يَوْمُ ٱلْفَصْلِ ٱلَّذِى كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
Hatha yawmu alfasli allatheekuntum bihi tukaththiboon
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
۞ ٱحْشُرُوا۟ ٱلَّذِينَ ظَلَمُوا۟ وَأَزْوَٰجَهُمْ وَمَا كَانُوا۟ يَعْبُدُونَ
Ohshuroo allatheena thalamoowaazwajahum wama kanoo yaAAbudoon
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهْدُوهُمْ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلْجَحِيمِ
Min dooni Allahi fahdoohum ilasirati aljaheem
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
وَقِفُوهُمْ ۖ إِنَّهُم مَّسْـُٔولُونَ
Waqifoohum innahum masooloon
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
مَا لَكُمْ لَا تَنَاصَرُونَ
Ma lakum la tanasaroon
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
بَلْ هُمُ ٱلْيَوْمَ مُسْتَسْلِمُونَ
Bal humu alyawma mustaslimoon
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
وَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَآءَلُونَ
Waaqbala baAAduhum AAala baAAdinyatasaaloon
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
قَالُوٓا۟ إِنَّكُمْ كُنتُمْ تَأْتُونَنَا عَنِ ٱلْيَمِينِ
Qaloo innakum kuntum ta/toonanaAAani alyameen
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
قَالُوا۟ بَل لَّمْ تَكُونُوا۟ مُؤْمِنِينَ
Qaloo bal lam takoonoo mu/mineen
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيْكُم مِّن سُلْطَـٰنٍۭ ۖ بَلْ كُنتُمْ قَوْمًا طَـٰغِينَ
Wama kana lanaAAalaykum min sultanin bal kuntum qawman tagheen
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
فَحَقَّ عَلَيْنَا قَوْلُ رَبِّنَآ ۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
Fahaqqa AAalayna qawlu rabbinainna latha-iqoon
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
فَأَغْوَيْنَـٰكُمْ إِنَّا كُنَّا غَـٰوِينَ
Faaghwaynakum inna kunnaghaween
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
فَإِنَّهُمْ يَوْمَئِذٍ فِى ٱلْعَذَابِ مُشْتَرِكُونَ
Fa-innahum yawma-ithin fee alAAathabimushtarikoon
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِٱلْمُجْرِمِينَ
Inna kathalika nafAAalu bilmujrimeen
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوٓا۟ إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَآ إِلَـٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ
Innahum kanoo itha qeela lahumla ilaha illa Allahu yastakbiroon
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓا۟ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٍ مَّجْنُونٍۭ
Wayaqooloona a-inna latarikoo alihatinalishaAAirin majnoon
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
بَلْ جَآءَ بِٱلْحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلْمُرْسَلِينَ
Bal jaa bilhaqqi wasaddaqaalmursaleen
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
إِنَّكُمْ لَذَآئِقُوا۟ ٱلْعَذَابِ ٱلْأَلِيمِ
Innakum latha-iqoo alAAathabial-aleem
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
وَمَا تُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
Wama tujzawna illa makuntum taAAmaloon
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلْمُخْلَصِينَ
Illa AAibada Allahialmukhlaseen
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
أُو۟لَـٰٓئِكَ لَهُمْ رِزْقٌ مَّعْلُومٌ
Ola-ika lahum rizqun maAAloom
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
فَوَٰكِهُ ۖ وَهُم مُّكْرَمُونَ
Fawakihu wahum mukramoon
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
فِى جَنَّـٰتِ ٱلنَّعِيمِ
Fee jannati annaAAeem
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
عَلَىٰ سُرُرٍ مُّتَقَـٰبِلِينَ
AAala sururin mutaqabileen
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍۭ
Yutafu AAalayhim bika/sin min maAAeen
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
بَيْضَآءَ لَذَّةٍ لِّلشَّـٰرِبِينَ
Baydaa laththatin lishsharibeen
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ
La feeha ghawlun walahum AAanha yunzafoon
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
وَعِندَهُمْ قَـٰصِرَٰتُ ٱلطَّرْفِ عِينٌ
WaAAindahum qasiratu attarfiAAeen
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
كَأَنَّهُنَّ بَيْضٌ مَّكْنُونٌ
Kaannahunna baydun maknoon
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَآءَلُونَ
Faaqbala baAAduhum AAala baAAdinyatasaaloon
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
قَالَ قَآئِلٌ مِّنْهُمْ إِنِّى كَانَ لِى قَرِينٌ
Qala qa-ilun minhum innee kanalee qareen
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلْمُصَدِّقِينَ
Yaqoolu a-innaka lamina almusaddiqeen
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
أَءِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَـٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
A-itha mitna wakunnaturaban waAAithaman a-innalamadeenoon
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
قَالَ هَلْ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
Qala hal antum muttaliAAoon
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِى سَوَآءِ ٱلْجَحِيمِ
FattalaAAa faraahu feesawa-i aljaheem
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرْدِينِ
Qala tallahi in kidtalaturdeen
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
وَلَوْلَا نِعْمَةُ رَبِّى لَكُنتُ مِنَ ٱلْمُحْضَرِينَ
Walawla niAAmatu rabbee lakuntu minaalmuhdareen
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
أَفَمَا نَحْنُ بِمَيِّتِينَ
Afama nahnu bimayyiteen
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
إِلَّا مَوْتَتَنَا ٱلْأُولَىٰ وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ
Illa mawtatana al-oolawama nahnu bimuAAaththabeen
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
إِنَّ هَـٰذَا لَهُوَ ٱلْفَوْزُ ٱلْعَظِيمُ
Inna hatha lahuwa alfawzu alAAatheem
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
لِمِثْلِ هَـٰذَا فَلْيَعْمَلِ ٱلْعَـٰمِلُونَ
Limithli hatha falyaAAmali alAAamiloon
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
أَذَٰلِكَ خَيْرٌ نُّزُلًا أَمْ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
Athalika khayrun nuzulan am shajaratuazzaqqoom
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
إِنَّا جَعَلْنَـٰهَا فِتْنَةً لِّلظَّـٰلِمِينَ
Inna jaAAalnahafitnatan liththalimeen
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
إِنَّهَا شَجَرَةٌ تَخْرُجُ فِىٓ أَصْلِ ٱلْجَحِيمِ
Innaha shajaratun takhruju fee aslialjaheem
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
طَلْعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَـٰطِينِ
TalAAuha kaannahu ruoosu ashshayateen
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
فَإِنَّهُمْ لَـَٔاكِلُونَ مِنْهَا فَمَالِـُٔونَ مِنْهَا ٱلْبُطُونَ
Fa-innahum laakiloona minhafamali-oona minha albutoon
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّ لَهُمْ عَلَيْهَا لَشَوْبًا مِّنْ حَمِيمٍ
Thumma inna lahum AAalayha lashawbanmin hameem
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّ مَرْجِعَهُمْ لَإِلَى ٱلْجَحِيمِ
Thumma inna marjiAAahum la-ila aljaheem
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
إِنَّهُمْ أَلْفَوْا۟ ءَابَآءَهُمْ ضَآلِّينَ
Innahum alfaw abaahum dalleen
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
فَهُمْ عَلَىٰٓ ءَاثَـٰرِهِمْ يُهْرَعُونَ
Fahum AAala atharihimyuhraAAoon
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
وَلَقَدْ ضَلَّ قَبْلَهُمْ أَكْثَرُ ٱلْأَوَّلِينَ
Walaqad dalla qablahum aktharual-awwaleen
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
Walaqad arsalna feehim munthireen
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
فَٱنظُرْ كَيْفَ كَانَ عَـٰقِبَةُ ٱلْمُنذَرِينَ
Fanthur kayfa kanaAAaqibatu almunthareen
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلْمُخْلَصِينَ
Illa AAibada Allahialmukhlaseen
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
وَلَقَدْ نَادَىٰنَا نُوحٌ فَلَنِعْمَ ٱلْمُجِيبُونَ
Walaqad nadana noohunfalaniAAma almujeeboon
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
وَنَجَّيْنَـٰهُ وَأَهْلَهُۥ مِنَ ٱلْكَرْبِ ٱلْعَظِيمِ
Wanajjaynahu waahlahu mina alkarbialAAatheem
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
وَجَعَلْنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلْبَاقِينَ
WajaAAalna thurriyyatahu humualbaqeen
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِى ٱلْـَٔاخِرِينَ
Watarakna AAalayhi fee al-akhireen
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
سَلَـٰمٌ عَلَىٰ نُوحٍ فِى ٱلْعَـٰلَمِينَ
Salamun AAala noohinfee alAAalameen
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ
Inna kathalika najzee almuhsineen
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُۥ مِنْ عِبَادِنَا ٱلْمُؤْمِنِينَ
Innahu min AAibadinaalmu/mineen
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
ثُمَّ أَغْرَقْنَا ٱلْـَٔاخَرِينَ
Thumma aghraqna al-akhareen
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبْرَٰهِيمَ
Wa-inna min sheeAAatihi la-ibraheem
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
إِذْ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
Ith jaa rabbahu biqalbinsaleem
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِۦ مَاذَا تَعْبُدُونَ
Ith qala li-abeehi waqawmihi mathataAAbudoon
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
أَئِفْكًا ءَالِهَةً دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
A-ifkan alihatan doona Allahitureedoon
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلْعَـٰلَمِينَ
Fama thannukum birabbialAAalameen
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
فَنَظَرَ نَظْرَةً فِى ٱلنُّجُومِ
Fanathara nathratanfee annujoom
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
فَقَالَ إِنِّى سَقِيمٌ
Faqala innee saqeem
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
فَتَوَلَّوْا۟ عَنْهُ مُدْبِرِينَ
Fatawallaw AAanhu mudbireen
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمْ فَقَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ
Faragha ila alihatihimfaqala ala ta/kuloon
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
مَا لَكُمْ لَا تَنطِقُونَ
Ma lakum la tantiqoon
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
فَرَاغَ عَلَيْهِمْ ضَرْبًۢا بِٱلْيَمِينِ
Faragha AAalayhim darban bilyameen
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
فَأَقْبَلُوٓا۟ إِلَيْهِ يَزِفُّونَ
Faaqbaloo ilayhi yaziffoon
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
قَالَ أَتَعْبُدُونَ مَا تَنْحِتُونَ
Qala ataAAbudoona ma tanhitoon
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمْ وَمَا تَعْمَلُونَ
Wallahu khalaqakum wamataAAmaloon
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
قَالُوا۟ ٱبْنُوا۟ لَهُۥ بُنْيَـٰنًا فَأَلْقُوهُ فِى ٱلْجَحِيمِ
Qaloo ibnoo lahu bunyananfaalqoohu fee aljaheem
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
فَأَرَادُوا۟ بِهِۦ كَيْدًا فَجَعَلْنَـٰهُمُ ٱلْأَسْفَلِينَ
Faaradoo bihi kaydan fajaAAalnahumual-asfaleen
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
وَقَالَ إِنِّى ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّى سَيَهْدِينِ
Waqala innee thahibun ilarabbee sayahdeen
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّـٰلِحِينَ
Rabbi hablee mina assaliheen
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
فَبَشَّرْنَـٰهُ بِغُلَـٰمٍ حَلِيمٍ
Fabashsharnahu bighulamin haleem
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَـٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَـٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّـٰبِرِينَ
Falamma balagha maAAahu assaAAyaqala ya bunayya innee ara fee almanamiannee athbahuka fanthur mathatara qala ya abati ifAAal ma tu/marusatajidunee in shaa Allahu mina assabireen
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
فَلَمَّآ أَسْلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلْجَبِينِ
Falamma aslama watallahuliljabeen
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
وَنَـٰدَيْنَـٰهُ أَن يَـٰٓإِبْرَٰهِيمُ
Wanadaynahu an ya ibraheem
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
قَدْ صَدَّقْتَ ٱلرُّءْيَآ ۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ
Qad saddaqta arru/yainna kathalika najzee almuhsineen
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّ هَـٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَـٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
Inna hatha lahuwa albalaoalmubeen
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
وَفَدَيْنَـٰهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ
Wafadaynahu bithibhinAAatheem
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِى ٱلْـَٔاخِرِينَ
Watarakna AAalayhi fee al-akhireen
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
سَلَـٰمٌ عَلَىٰٓ إِبْرَٰهِيمَ
Salamun AAala ibraheem
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ
Kathalika najzee almuhsineen
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُۥ مِنْ عِبَادِنَا ٱلْمُؤْمِنِينَ
Innahu min AAibadinaalmu/mineen
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
وَبَشَّرْنَـٰهُ بِإِسْحَـٰقَ نَبِيًّا مِّنَ ٱلصَّـٰلِحِينَ
Wabashsharnahu bi-ishaqanabiyyan mina assaliheen
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
وَبَـٰرَكْنَا عَلَيْهِ وَعَلَىٰٓ إِسْحَـٰقَ ۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحْسِنٌ وَظَالِمٌ لِّنَفْسِهِۦ مُبِينٌ
Wabarakna AAalayhi waAAalaishaqa wamin thurriyyatihima muhsinunwathalimun linafsihi mubeen
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
وَلَقَدْ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَـٰرُونَ
Walaqad mananna AAala moosawaharoon
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
وَنَجَّيْنَـٰهُمَا وَقَوْمَهُمَا مِنَ ٱلْكَرْبِ ٱلْعَظِيمِ
Wanajjaynahuma waqawmahumamina alkarbi alAAatheem
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
وَنَصَرْنَـٰهُمْ فَكَانُوا۟ هُمُ ٱلْغَـٰلِبِينَ
Wanasarnahum fakanoohumu alghalibeen
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
وَءَاتَيْنَـٰهُمَا ٱلْكِتَـٰبَ ٱلْمُسْتَبِينَ
Waataynahuma alkitabaalmustabeen
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
وَهَدَيْنَـٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلْمُسْتَقِيمَ
Wahadaynahuma assirataalmustaqeem
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِمَا فِى ٱلْـَٔاخِرِينَ
Watarakna AAalayhima fee al-akhireen
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
سَلَـٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَـٰرُونَ
Salamun AAala moosawaharoon
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ
Inna kathalika najzee almuhsineen
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُمَا مِنْ عِبَادِنَا ٱلْمُؤْمِنِينَ
Innahuma min AAibadinaalmu/mineen
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ
Wa-inna ilyasa lamina almursaleen
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
Ith qala liqawmihi alatattaqoon
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
أَتَدْعُونَ بَعْلًا وَتَذَرُونَ أَحْسَنَ ٱلْخَـٰلِقِينَ
AtadAAoona baAAlan watatharoona ahsanaalkhaliqeen
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
ٱللَّهَ رَبَّكُمْ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلْأَوَّلِينَ
Allaha rabbakum warabba aba-ikumual-awwaleen
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ
Fakaththaboohu fa-innahum lamuhdaroon
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلْمُخْلَصِينَ
Illa AAibada Allahialmukhlaseen
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِى ٱلْـَٔاخِرِينَ
Watarakna AAalayhi fee al-akhireen
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
سَلَـٰمٌ عَلَىٰٓ إِلْ يَاسِينَ
Salamun AAala il yaseen
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ
Inna kathalika najzee almuhsineen
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُۥ مِنْ عِبَادِنَا ٱلْمُؤْمِنِينَ
Innahu min AAibadinaalmu/mineen
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ
Wa-inna lootan lamina almursaleen
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ نَجَّيْنَـٰهُ وَأَهْلَهُۥٓ أَجْمَعِينَ
Ith najjaynahu waahlahuajmaAAeen
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
إِلَّا عَجُوزًا فِى ٱلْغَـٰبِرِينَ
Illa AAajoozan fee alghabireen
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
ثُمَّ دَمَّرْنَا ٱلْـَٔاخَرِينَ
Thumma dammarna al-akhareen
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
وَإِنَّكُمْ لَتَمُرُّونَ عَلَيْهِم مُّصْبِحِينَ
Wa-innakum latamurroona AAalayhim musbiheen
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
وَبِٱلَّيْلِ ۗ أَفَلَا تَعْقِلُونَ
Wabillayli afala taAAqiloon
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلْمُرْسَلِينَ
Wa-inna yoonusa lamina almursaleen
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ أَبَقَ إِلَى ٱلْفُلْكِ ٱلْمَشْحُونِ
Ith abaqa ila alfulki almashhoon
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلْمُدْحَضِينَ
Fasahama fakana mina almudhadeen
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
فَٱلْتَقَمَهُ ٱلْحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٌ
Faltaqamahu alhootu wahuwamuleem
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
فَلَوْلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلْمُسَبِّحِينَ
Falawla annahu kana minaalmusabbiheen
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
لَلَبِثَ فِى بَطْنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
Lalabitha fee batnihi ilayawmi yubAAathoon
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
۞ فَنَبَذْنَـٰهُ بِٱلْعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٌ
Fanabathnahu bilAAara-iwahuwa saqeem
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
وَأَنۢبَتْنَا عَلَيْهِ شَجَرَةً مِّن يَقْطِينٍ
Waanbatna AAalayhi shajaratan minyaqteen
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
وَأَرْسَلْنَـٰهُ إِلَىٰ مِا۟ئَةِ أَلْفٍ أَوْ يَزِيدُونَ
Waarsalnahu ila mi-ati alfinaw yazeedoon
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
فَـَٔامَنُوا۟ فَمَتَّعْنَـٰهُمْ إِلَىٰ حِينٍ
Faamanoo famattaAAnahum ilaheen
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
فَٱسْتَفْتِهِمْ أَلِرَبِّكَ ٱلْبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلْبَنُونَ
Fastaftihim alirabbika albanatuwalahumu albanoon
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
أَمْ خَلَقْنَا ٱلْمَلَـٰٓئِكَةَ إِنَـٰثًا وَهُمْ شَـٰهِدُونَ
Am khalaqna almala-ikata inathanwahum shahidoon
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
أَلَآ إِنَّهُم مِّنْ إِفْكِهِمْ لَيَقُولُونَ
Ala innahum min ifkihim layaqooloon
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَـٰذِبُونَ
Walada Allahu wa-innahum lakathiboon
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
أَصْطَفَى ٱلْبَنَاتِ عَلَى ٱلْبَنِينَ
Astafa albanati AAalaalbaneen
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ
Ma lakum kayfa tahkumoon
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
Afala tathakkaroon
አትገነዘቡምን?
أَمْ لَكُمْ سُلْطَـٰنٌ مُّبِينٌ
Am lakum sultanun mubeen
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
فَأْتُوا۟ بِكِتَـٰبِكُمْ إِن كُنتُمْ صَـٰدِقِينَ
Fa/too bikitabikum in kuntum sadiqeen
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
وَجَعَلُوا۟ بَيْنَهُۥ وَبَيْنَ ٱلْجِنَّةِ نَسَبًا ۚ وَلَقَدْ عَلِمَتِ ٱلْجِنَّةُ إِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ
WajaAAaloo baynahu wabayna aljinnatinasaban walaqad AAalimati aljinnatu innahum lamuhdaroon
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
سُبْحَـٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
Subhana Allahi AAammayasifoon
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلْمُخْلَصِينَ
Illa AAibada Allahialmukhlaseen
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
فَإِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ
Fa-innakum wama taAAbudoon
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
مَآ أَنتُمْ عَلَيْهِ بِفَـٰتِنِينَ
Ma antum AAalayhi bifatineen
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
إِلَّا مَنْ هُوَ صَالِ ٱلْجَحِيمِ
Illa man huwa sali aljaheem
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٌ مَّعْلُومٌ
Wama minna illa lahumaqamun maAAloom
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
وَإِنَّا لَنَحْنُ ٱلصَّآفُّونَ
Wa-inna lanahnu assaffoon
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
وَإِنَّا لَنَحْنُ ٱلْمُسَبِّحُونَ
Wa-inna lanahnu almusabbihoon
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
وَإِن كَانُوا۟ لَيَقُولُونَ
Wa-in kanoo layaqooloon
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
لَوْ أَنَّ عِندَنَا ذِكْرًا مِّنَ ٱلْأَوَّلِينَ
Law anna AAindana thikranmina al-awwaleen
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلْمُخْلَصِينَ
Lakunna AAibada Allahialmukhlaseen
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
فَكَفَرُوا۟ بِهِۦ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ
Fakafaroo bihi fasawfa yaAAlamoon
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
وَلَقَدْ سَبَقَتْ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلْمُرْسَلِينَ
Walaqad sabaqat kalimatuna liAAibadinaalmursaleen
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
إِنَّهُمْ لَهُمُ ٱلْمَنصُورُونَ
Innahum lahumu almansooroon
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلْغَـٰلِبُونَ
Wa-inna jundana lahumu alghaliboon
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
فَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ
Fatawalla AAanhum hatta heen
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
وَأَبْصِرْهُمْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ
Waabsirhum fasawfa yubsiroon
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ
AfabiAAathabina yastaAAjiloon
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمْ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلْمُنذَرِينَ
Fa-itha nazala bisahatihimfasaa sabahu almunthareen
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
وَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ
Watawalla AAanhum hatta heen
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
وَأَبْصِرْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ
Waabsir fasawfa yubsiroon
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
سُبْحَـٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
Subhana rabbika rabbi alAAizzatiAAamma yasifoon
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
وَسَلَـٰمٌ عَلَى ٱلْمُرْسَلِينَ
Wasalamun AAala almursaleen
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
وَٱلْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَـٰلَمِينَ
Walhamdu lillahirabbi alAAalameen
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡