وَٱلنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ
Wannajmi itha hawa
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
The Star
وَٱلنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ
Wannajmi itha hawa
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَىٰ
Ma dalla sahibukum wamaghawa
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلْهَوَىٰٓ
Wama yantiqu AAani alhawa
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْىٌ يُوحَىٰ
In huwa illa wahyun yooha
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلْقُوَىٰ
AAallamahu shadeedu alquwa
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
ذُو مِرَّةٍ فَٱسْتَوَىٰ
Thoo mirratin fastawa
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
وَهُوَ بِٱلْأُفُقِ ٱلْأَعْلَىٰ
Wahuwa bil-ofuqi al-aAAla
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
Thumma dana fatadalla
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ
Fakana qaba qawsayni aw adna
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
فَأَوْحَىٰٓ إِلَىٰ عَبْدِهِۦ مَآ أَوْحَىٰ
Faawha ila AAabdihi maawha
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
مَا كَذَبَ ٱلْفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
Ma kathaba alfu-adu maraa
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
أَفَتُمَـٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
Afatumaroonahu AAala mayara
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
وَلَقَدْ رَءَاهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ
Walaqad raahu nazlatan okhra
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
عِندَ سِدْرَةِ ٱلْمُنتَهَىٰ
AAinda sidrati almuntaha
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلْمَأْوَىٰٓ
AAindaha jannatu alma/wa
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
إِذْ يَغْشَى ٱلسِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ
Ith yaghsha assidratama yaghsha
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
مَا زَاغَ ٱلْبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
Ma zagha albasaru wamatagha
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ ءَايَـٰتِ رَبِّهِ ٱلْكُبْرَىٰٓ
Laqad raa min ayatirabbihi alkubra
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
أَفَرَءَيْتُمُ ٱللَّـٰتَ وَٱلْعُزَّىٰ
Afaraaytumu allata walAAuzza
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلْأُخْرَىٰٓ
Wamanata aththalithataal-okhra
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلْأُنثَىٰ
Alakumu aththakaru walahual-ontha
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰٓ
Tilka ithan qismatun deeza
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡
إِنْ هِىَ إِلَّآ أَسْمَآءٌ سَمَّيْتُمُوهَآ أَنتُمْ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَـٰنٍ ۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهْوَى ٱلْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلْهُدَىٰٓ
In hiya illa asmaonsammaytumooha antum waabaokum maanzala Allahu biha min sultanin inyattabiAAoona illa aththanna wamatahwa al-anfusu walaqad jaahum min rabbihimu alhuda
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
أَمْ لِلْإِنسَـٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
Am lil-insani ma tamanna
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
فَلِلَّهِ ٱلْـَٔاخِرَةُ وَٱلْأُولَىٰ
Falillahi al-akhiratu wal-oola
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِى ٱلسَّمَـٰوَٰتِ لَا تُغْنِى شَفَـٰعَتُهُمْ شَيْـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعْدِ أَن يَأْذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرْضَىٰٓ
Wakam min malakin fee assamawatila tughnee shafaAAatuhum shay-an illa minbaAAdi an ya/thana Allahu liman yashao wayarda
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِٱلْـَٔاخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلْمَلَـٰٓئِكَةَ تَسْمِيَةَ ٱلْأُنثَىٰ
Inna allatheena la yu/minoonabil-akhirati layusammoona almala-ikatatasmiyata al-ontha
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنْ عِلْمٍ ۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ ۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغْنِى مِنَ ٱلْحَقِّ شَيْـًٔا
Wama lahum bihi min AAilmin inyattabiAAoona illa aththanna wa-innaaththanna la yughnee mina alhaqqishay-a
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
فَأَعْرِضْ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكْرِنَا وَلَمْ يُرِدْ إِلَّا ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا
FaaAArid AAan man tawalla AAanthikrina walam yurid illa alhayataaddunya
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
ذَٰلِكَ مَبْلَغُهُم مِّنَ ٱلْعِلْمِ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ ٱهْتَدَىٰ
Thalika mablaghuhum mina alAAilmiinna rabbaka huwa aAAlamu biman dalla AAan sabeelihiwahuwa aAAlamu bimani ihtada
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
وَلِلَّهِ مَا فِى ٱلسَّمَـٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ لِيَجْزِىَ ٱلَّذِينَ أَسَـٰٓـُٔوا۟ بِمَا عَمِلُوا۟ وَيَجْزِىَ ٱلَّذِينَ أَحْسَنُوا۟ بِٱلْحُسْنَى
Walillahi ma fee assamawatiwama fee al-ardi liyajziya allatheena asaoobima AAamiloo wayajziya allatheena ahsanoobilhusna
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡
ٱلَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَـٰٓئِرَ ٱلْإِثْمِ وَٱلْفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلْمَغْفِرَةِ ۚ هُوَ أَعْلَمُ بِكُمْ إِذْ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلْأَرْضِ وَإِذْ أَنتُمْ أَجِنَّةٌ فِى بُطُونِ أُمَّهَـٰتِكُمْ ۖ فَلَا تُزَكُّوٓا۟ أَنفُسَكُمْ ۖ هُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
Allatheena yajtaniboona kaba-iraal-ithmi walfawahisha illa allamama innarabbaka wasiAAu almaghfirati huwa aAAlamu bikum ithanshaakum mina al-ardi wa-ith antum ajinnatun feebutooni ommahatikum fala tuzakkoo anfusakumhuwa aAAlamu bimani ittaqa
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
أَفَرَءَيْتَ ٱلَّذِى تَوَلَّىٰ
Afaraayta allathee tawalla
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
وَأَعْطَىٰ قَلِيلًا وَأَكْدَىٰٓ
WaaAAta qaleelan waakda
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
أَعِندَهُۥ عِلْمُ ٱلْغَيْبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
aAAindahu AAilmu alghaybi fahuwa yara
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
أَمْ لَمْ يُنَبَّأْ بِمَا فِى صُحُفِ مُوسَىٰ
Am lam yunabba/ bima fee suhufimoosa
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
وَإِبْرَٰهِيمَ ٱلَّذِى وَفَّىٰٓ
Wa-ibraheema allathee waffa
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ
Alla taziru waziratun wizraokhra
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَـٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
Waan laysa lil-insani illa masaAAa
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
وَأَنَّ سَعْيَهُۥ سَوْفَ يُرَىٰ
Waanna saAAyahu sawfa yura
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
ثُمَّ يُجْزَىٰهُ ٱلْجَزَآءَ ٱلْأَوْفَىٰ
Thumma yujzahu aljazaa al-awfa
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلْمُنتَهَىٰ
Waanna ila rabbika almuntaha
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضْحَكَ وَأَبْكَىٰ
Waannahu huwa adhaka waabka
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحْيَا
Waannahu huwa amata waahya
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوْجَيْنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰ
Waannahu khalaqa azzawjayni aththakarawal-ontha
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
مِن نُّطْفَةٍ إِذَا تُمْنَىٰ
Min nutfatin itha tumna
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
وَأَنَّ عَلَيْهِ ٱلنَّشْأَةَ ٱلْأُخْرَىٰ
Waanna AAalayhi annash-ata al-okhra
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغْنَىٰ وَأَقْنَىٰ
Waannahu huwa aghna waaqna
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعْرَىٰ
Waannahu huwa rabbu ashshiAAra
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
وَأَنَّهُۥٓ أَهْلَكَ عَادًا ٱلْأُولَىٰ
Waannahu ahlaka AAadan al-oola
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
وَثَمُودَا۟ فَمَآ أَبْقَىٰ
Wathamooda fama abqa
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
وَقَوْمَ نُوحٍ مِّن قَبْلُ ۖ إِنَّهُمْ كَانُوا۟ هُمْ أَظْلَمَ وَأَطْغَىٰ
Waqawma noohin min qablu innahum kanoohum athlama waatgha
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
وَٱلْمُؤْتَفِكَةَ أَهْوَىٰ
Walmu/tafikata ahwa
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
Faghashshaha ma ghashsha
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
فَبِأَىِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
Fabi-ayyi ala-i rabbika tatamara
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
هَـٰذَا نَذِيرٌ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلْأُولَىٰٓ
Hatha natheerun mina annuthurial-oola
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
أَزِفَتِ ٱلْـَٔازِفَةُ
Azifati al-azifat
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
لَيْسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
Laysa laha min dooni Allahi kashifat
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
أَفَمِنْ هَـٰذَا ٱلْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ
Afamin hatha alhadeethitaAAjaboon
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ
Watadhakoona wala tabkoon
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
وَأَنتُمْ سَـٰمِدُونَ
Waantum samidoon
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
فَٱسْجُدُوا۟ لِلَّهِ وَٱعْبُدُوا۟ ۩
Fasjudoo lillahi waAAbudoo
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡