إِذَا وَقَعَتِ ٱلْوَاقِعَةُ
Itha waqaAAati alwaqiAAat
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
The Inevitable
إِذَا وَقَعَتِ ٱلْوَاقِعَةُ
Itha waqaAAati alwaqiAAat
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ
Laysa liwaqAAatiha kathiba
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
خَافِضَةٌ رَّافِعَةٌ
Khafidatun rafiAAa
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
إِذَا رُجَّتِ ٱلْأَرْضُ رَجًّا
Itha rujjati al-ardu rajja
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
وَبُسَّتِ ٱلْجِبَالُ بَسًّا
Wabussati aljibalu bassa
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
فَكَانَتْ هَبَآءً مُّنۢبَثًّا
Fakanat habaan munbaththa
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
وَكُنتُمْ أَزْوَٰجًا ثَلَـٰثَةً
Wakuntum azwajan thalatha
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
فَأَصْحَـٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ مَآ أَصْحَـٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ
Faas-habu almaymanati maas-habu almaymanat
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَأَصْحَـٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ مَآ أَصْحَـٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ
Waas-habu almash-amati maas-habu almash-amat
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
وَٱلسَّـٰبِقُونَ ٱلسَّـٰبِقُونَ
Wassabiqoona assabiqoon
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
أُو۟لَـٰٓئِكَ ٱلْمُقَرَّبُونَ
Ola-ika almuqarraboon
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
فِى جَنَّـٰتِ ٱلنَّعِيمِ
Fee jannati annaAAeem
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
ثُلَّةٌ مِّنَ ٱلْأَوَّلِينَ
Thullatun mina al-awwaleen
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَقَلِيلٌ مِّنَ ٱلْـَٔاخِرِينَ
Waqaleelun mina al-akhireena
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
عَلَىٰ سُرُرٍ مَّوْضُونَةٍ
AAala sururin mawdoona
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيْهَا مُتَقَـٰبِلِينَ
Muttaki-eena AAalayha mutaqabileen
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَٰنٌ مُّخَلَّدُونَ
Yatoofu AAalayhim wildanunmukhalladoon
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
Bi-akwabin waabareeqa waka/sinmin maAAeen
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
La yusaddaAAoona AAanhawala yunzifoon
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
وَفَـٰكِهَةٍ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
Wafakihatin mimmayatakhayyaroon
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
وَلَحْمِ طَيْرٍ مِّمَّا يَشْتَهُونَ
Walahmi tayrin mimmayashtahoon
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
وَحُورٌ عِينٌ
Wahoorun AAeen
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
كَأَمْثَـٰلِ ٱللُّؤْلُؤِ ٱلْمَكْنُونِ
Kaamthali allu/lui almaknoon
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
جَزَآءًۢ بِمَا كَانُوا۟ يَعْمَلُونَ
Jazaan bima kanooyaAAmaloon
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا تَأْثِيمًا
La yasmaAAoona feeha laghwanwala ta/theema
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
إِلَّا قِيلًا سَلَـٰمًا سَلَـٰمًا
Illa qeelan salaman salama
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
وَأَصْحَـٰبُ ٱلْيَمِينِ مَآ أَصْحَـٰبُ ٱلْيَمِينِ
Waas-habu alyameeni maas-habu alyameen
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
فِى سِدْرٍ مَّخْضُودٍ
Fee sidrin makhdood
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
وَطَلْحٍ مَّنضُودٍ
Watalhin mandood
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
وَظِلٍّ مَّمْدُودٍ
Wathillin mamdood
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
وَمَآءٍ مَّسْكُوبٍ
Wama-in maskoob
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
وَفَـٰكِهَةٍ كَثِيرَةٍ
Wafakihatin katheera
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
لَّا مَقْطُوعَةٍ وَلَا مَمْنُوعَةٍ
La maqtooAAatin walamamnooAAa
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
وَفُرُشٍ مَّرْفُوعَةٍ
Wafurushin marfooAAa
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
إِنَّآ أَنشَأْنَـٰهُنَّ إِنشَآءً
Inna ansha/nahunna inshaa
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
فَجَعَلْنَـٰهُنَّ أَبْكَارًا
FajaAAalnahunna abkara
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
عُرُبًا أَتْرَابًا
AAuruban atraba
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
لِّأَصْحَـٰبِ ٱلْيَمِينِ
Li-as-habi alyameen
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
ثُلَّةٌ مِّنَ ٱلْأَوَّلِينَ
Thullatun mina al-awwaleen
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَثُلَّةٌ مِّنَ ٱلْـَٔاخِرِينَ
Wathullatun mina al-akhireen
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَأَصْحَـٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصْحَـٰبُ ٱلشِّمَالِ
Waas-habu ashshimalima as-habu ashshimal
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
فِى سَمُومٍ وَحَمِيمٍ
Fee samoomin wahameem
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
وَظِلٍّ مِّن يَحْمُومٍ
Wathillin min yahmoom
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
لَّا بَارِدٍ وَلَا كَرِيمٍ
La baridin wala kareem
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا۟ قَبْلَ ذَٰلِكَ مُتْرَفِينَ
Innahum kanoo qabla thalikamutrafeen
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
وَكَانُوا۟ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلْحِنثِ ٱلْعَظِيمِ
Wakanoo yusirroona AAalaalhinthi alAAatheem
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
وَكَانُوا۟ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَـٰمًا أَءِنَّا لَمَبْعُوثُونَ
Wakanoo yaqooloona a-itha mitnawakunna turaban waAAithamana-inna lamabAAoothoon
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلْأَوَّلُونَ
Awa abaona al-awwaloon
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
قُلْ إِنَّ ٱلْأَوَّلِينَ وَٱلْـَٔاخِرِينَ
Qul inna al-awwaleena wal-akhireen
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
لَمَجْمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَـٰتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ
LamajmooAAoona ila meeqatiyawmin maAAloom
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّكُمْ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلْمُكَذِّبُونَ
Thumma innakum ayyuha addalloonaalmukaththiboon
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
لَـَٔاكِلُونَ مِن شَجَرٍ مِّن زَقُّومٍ
Laakiloona min shajarin min zaqqoom
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
فَمَالِـُٔونَ مِنْهَا ٱلْبُطُونَ
Famali-oona minha albutoon
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
فَشَـٰرِبُونَ عَلَيْهِ مِنَ ٱلْحَمِيمِ
Fashariboona AAalayhi mina alhameem
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
فَشَـٰرِبُونَ شُرْبَ ٱلْهِيمِ
Fashariboona shurba alheem
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
هَـٰذَا نُزُلُهُمْ يَوْمَ ٱلدِّينِ
Hatha nuzuluhum yawma addeen
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
نَحْنُ خَلَقْنَـٰكُمْ فَلَوْلَا تُصَدِّقُونَ
Nahnu khalaqnakum falawlatusaddiqoon
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
أَفَرَءَيْتُم مَّا تُمْنُونَ
Afaraaytum ma tumnoon
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
ءَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُۥٓ أَمْ نَحْنُ ٱلْخَـٰلِقُونَ
Aantum takhluqoonahu am nahnu alkhaliqoon
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
نَحْنُ قَدَّرْنَا بَيْنَكُمُ ٱلْمَوْتَ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ
Nahnu qaddarna baynakumualmawta wama nahnu bimasbooqeen
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمْثَـٰلَكُمْ وَنُنشِئَكُمْ فِى مَا لَا تَعْلَمُونَ
AAala an nubaddila amthalakumwanunshi-akum fee ma la taAAlamoon
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ ٱلنَّشْأَةَ ٱلْأُولَىٰ فَلَوْلَا تَذَكَّرُونَ
Walaqad AAalimtumu annash-ata al-oolafalawla tathakkaroon
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
أَفَرَءَيْتُم مَّا تَحْرُثُونَ
Afaraaytum ma tahruthoon
የምትዘሩትንም አያችሁን?
ءَأَنتُمْ تَزْرَعُونَهُۥٓ أَمْ نَحْنُ ٱلزَّٰرِعُونَ
Aantum tazraAAoonahu am nahnu azzariAAoon
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
لَوْ نَشَآءُ لَجَعَلْنَـٰهُ حُطَـٰمًا فَظَلْتُمْ تَفَكَّهُونَ
Law nashao lajaAAalnahu hutamanfathaltum tafakkahoon
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
إِنَّا لَمُغْرَمُونَ
Inna lamughramoon
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ
Bal nahnu mahroomoon
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
أَفَرَءَيْتُمُ ٱلْمَآءَ ٱلَّذِى تَشْرَبُونَ
Afaraaytumu almaa allatheetashraboon
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
ءَأَنتُمْ أَنزَلْتُمُوهُ مِنَ ٱلْمُزْنِ أَمْ نَحْنُ ٱلْمُنزِلُونَ
Aantum anzaltumoohu mina almuzni am nahnualmunziloon
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
لَوْ نَشَآءُ جَعَلْنَـٰهُ أُجَاجًا فَلَوْلَا تَشْكُرُونَ
Law nashao jaAAalnahu ojajanfalawla tashkuroon
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
أَفَرَءَيْتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِى تُورُونَ
Afaraaytumu annara allateetooroon
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
ءَأَنتُمْ أَنشَأْتُمْ شَجَرَتَهَآ أَمْ نَحْنُ ٱلْمُنشِـُٔونَ
Aantum ansha/tum shajarataha am nahnualmunshi-oon
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
نَحْنُ جَعَلْنَـٰهَا تَذْكِرَةً وَمَتَـٰعًا لِّلْمُقْوِينَ
Nahnu jaAAalnaha tathkiratanwamataAAan lilmuqween
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
فَسَبِّحْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلْعَظِيمِ
Fasabbih bismi rabbika alAAatheem
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
۞ فَلَآ أُقْسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ
Fala oqsimu bimawaqiAAi annujoom
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٌ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ
Wa-innahu laqasamun law taAAlamoona AAatheem
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
إِنَّهُۥ لَقُرْءَانٌ كَرِيمٌ
Innahu laqur-anun kareem
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
فِى كِتَـٰبٍ مَّكْنُونٍ
Fee kitabin maknoon
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلْمُطَهَّرُونَ
La yamassuhu illa almutahharoon
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ ٱلْعَـٰلَمِينَ
Tanzeelun min rabbi alAAalameen
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
أَفَبِهَـٰذَا ٱلْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ
Afabihatha alhadeethi antummudhinoon
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ
WatajAAaloona rizqakum annakum tukaththiboon
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
فَلَوْلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلْحُلْقُومَ
Falawla itha balaghati alhulqoom
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
وَأَنتُمْ حِينَئِذٍ تَنظُرُونَ
Waantum heena-ithin tanthuroona
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنكُمْ وَلَـٰكِن لَّا تُبْصِرُونَ
Wanahnu aqrabu ilayhi minkum walakinla tubsiroon
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
فَلَوْلَآ إِن كُنتُمْ غَيْرَ مَدِينِينَ
Falawla in kuntum ghayra madeeneen
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
تَرْجِعُونَهَآ إِن كُنتُمْ صَـٰدِقِينَ
TarjiAAoonaha in kuntum sadiqeen
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلْمُقَرَّبِينَ
Faamma in kana minaalmuqarrabeen
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
فَرَوْحٌ وَرَيْحَانٌ وَجَنَّتُ نَعِيمٍ
Farawhun warayhanun wajannatunaAAeem
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنْ أَصْحَـٰبِ ٱلْيَمِينِ
Waamma in kana min as-habialyameen
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
فَسَلَـٰمٌ لَّكَ مِنْ أَصْحَـٰبِ ٱلْيَمِينِ
Fasalamun laka min as-habialyameen
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلْمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ
Waamma in kana mina almukaththibeenaaddalleen
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
فَنُزُلٌ مِّنْ حَمِيمٍ
Fanuzulun min hameem
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
وَتَصْلِيَةُ جَحِيمٍ
Watasliyatu jaheem
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
إِنَّ هَـٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلْيَقِينِ
Inna hatha lahuwa haqqualyaqeen
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
فَسَبِّحْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلْعَظِيمِ
Fasabbih bismi rabbika alAAatheem
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡