لَآ أُقْسِمُ بِيَوْمِ ٱلْقِيَـٰمَةِ
La oqsimu biyawmi alqiyamat
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
The Resurrection
لَآ أُقْسِمُ بِيَوْمِ ٱلْقِيَـٰمَةِ
La oqsimu biyawmi alqiyamat
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
وَلَآ أُقْسِمُ بِٱلنَّفْسِ ٱللَّوَّامَةِ
Wala oqsimu binnafsi allawwamat
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَـٰنُ أَلَّن نَّجْمَعَ عِظَامَهُۥ
Ayahsabu al-insanu allannajmaAAa AAithamah
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
بَلَىٰ قَـٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّىَ بَنَانَهُۥ
Bala qadireena AAala annusawwiya bananah
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
بَلْ يُرِيدُ ٱلْإِنسَـٰنُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُۥ
Bal yureedu al-insanu liyafjura amamah
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
يَسْـَٔلُ أَيَّانَ يَوْمُ ٱلْقِيَـٰمَةِ
Yas-alu ayyana yawmu alqiyama
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
فَإِذَا بَرِقَ ٱلْبَصَرُ
Fa-itha bariqa albasar
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
وَخَسَفَ ٱلْقَمَرُ
Wakhasafa alqamar
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
وَجُمِعَ ٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ
WajumiAAa ashshamsu walqamar
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
يَقُولُ ٱلْإِنسَـٰنُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ ٱلْمَفَرُّ
Yaqoolu al-insanu yawma-ithinayna almafar
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
كَلَّا لَا وَزَرَ
Kalla la wazar
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمُسْتَقَرُّ
Ila rabbika yawma-ithinalmustaqar
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
يُنَبَّؤُا۟ ٱلْإِنسَـٰنُ يَوْمَئِذٍۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
Yunabbao al-insanu yawma-ithinbima qaddama waakhkhar
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
بَلِ ٱلْإِنسَـٰنُ عَلَىٰ نَفْسِهِۦ بَصِيرَةٌ
Bali al-insanu AAala nafsihibaseera
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
وَلَوْ أَلْقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
Walaw alqa maAAatheerah
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
لَا تُحَرِّكْ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِۦٓ
La tuharrik bihi lisanakalitaAAjala bih
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُۥ وَقُرْءَانَهُۥ
Inna AAalayna jamAAahu waqur-anah
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
فَإِذَا قَرَأْنَـٰهُ فَٱتَّبِعْ قُرْءَانَهُۥ
Fa-itha qara/nahu fattabiAAqur-anah
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُۥ
Thumma inna AAalayna bayanah
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ ٱلْعَاجِلَةَ
Kalla bal tuhibboona alAAajila
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
وَتَذَرُونَ ٱلْـَٔاخِرَةَ
Watatharoona al-akhira
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ نَّاضِرَةٌ
Wujoohun yawma-ithin nadira
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌ
Ila rabbiha nathira
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍۭ بَاسِرَةٌ
Wawujoohun yawma-ithin basira
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌ
Tathunnu an yufAAala bihafaqira
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِىَ
Kalla itha balaghati attaraqiy
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
وَقِيلَ مَنْ ۜ رَاقٍ
Waqeela man raq
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلْفِرَاقُ
Wathanna annahu alfiraq
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
وَٱلْتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
Waltaffati assaqu bilssaq
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ ٱلْمَسَاقُ
Ila rabbika yawma-ithin almasaq
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
Fala saddaqa wala salla
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
وَلَـٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
Walakin kaththaba watawalla
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
Thumma thahaba ila ahlihiyatamatta
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ
Awla laka faawla
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
ثُمَّ أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰٓ
Thumma awla laka faawla
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
أَيَحْسَبُ ٱلْإِنسَـٰنُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
Ayahsabu al-insanu an yutrakasuda
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
أَلَمْ يَكُ نُطْفَةً مِّن مَّنِىٍّ يُمْنَىٰ
Alam yaku nutfatan min manayyin yumna
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةً فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
Thumma kana AAalaqatan fakhalaqafasawwa
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
فَجَعَلَ مِنْهُ ٱلزَّوْجَيْنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ
FajaAAala minhu azzawjayni aththakarawal-ontha
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
أَلَيْسَ ذَٰلِكَ بِقَـٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحْـِۧىَ ٱلْمَوْتَىٰ
Alaysa thalika biqadirin AAalaan yuhyiya almawta
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?